ሙሉዋ ጨረቃ
ሙሉዋ ጨረቃ-ብሩኅ ነሽ ደማቃ
ታለቅሳለች ነፍሴ-ተስፋ ትቆርጥና
በውበትሽ ተማርካ-በመራቅሽ አዝና
ብሆን ከወለሉ አንቺም ጣሪያ ላይ
ዝቅዝቅ ከሚያዩትስ የሚያምር የለም ወይ?????
አንገትን ሲያቀኑ ብቻ ነው ማማሩ??
ያም ይሄም ያም ይሄም አይንን ማጭርበሩ?
ፈክቶ መታየቱ ሽልምልም ማለቱ
በሩቅ ማጉዋጉዋቱ…………
ላይንም ሌላ አይን አለው
….
አንድን ጥሪኝ አፈር–ድንጋይ ብሎ ሚያስጥል በየጉራንጉሩ
ወርቅ ብሎ ሚያስቁዋጥር በየማህደሩ
እኔው ብሆን ነው ወይ የአይኔ አይን ባሪያ
ሳውቀው መሆንሽን የሌሎች አምሳያ
ጉልላት ያረኩሽ የፍጥረት እናት
በእውን የምትሞቂ ድንቅ የህልም እሳት
ዳኛ ነው የሚፈርድ ምክንያት ጠቃቅሶ መጽሃፍ አንብቦ
ግን ከሳሽ ተከሳሽ (ያው እንደኔና እንዳንቺው)
ስሜቱን አንግቦ
እእምሮው ረግቦ
አውቃለሁ እንዳይሻር ይህ የብሉይ አዋጅ
ከአለኝታዬ አይጃጅ
በምኞቴ አይዋጅ
እንደነበር ሊኖር መታከት ….. መታከት …….መታከት
ነውንጂ……
ነውናም ስገብር ለአዋጁ ለእጣዬ
አንቺ ዝቅ ብለሽ ወይ እኔ ከፍ ብዬ
“እንገናኝ ይሆን?????” ሆኑዋል ጥያቄዬ
`1961 ዓ.ም
ደበበ ሰይፉ
ለራስ የተፃፈ ደብዳቤ
No comments yet.
Leave a comment
-
Archives
- June 2009 (1)
- May 2009 (2)
- March 2009 (2)
- February 2009 (6)
- January 2009 (3)
- July 2008 (2)
- June 2008 (5)
-
Categories
-
RSS
Entries RSS
Comments RSS
